Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Blog

CERPHI

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ጤና ጥበቃ ሥርዓቱን ለማሻሻል ያለመ የዘርፈ ብዙ ባለሙያዎች የአንድ ጤና ጽንሰ-ሀሰብ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መድረክ እየተካሄደ ነው።

መጋቢት 08/2018 ዓ.ም – ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ግብርና ኮሙኒኬሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ጤና ጥበቃ ሥርዓቱን ለማሻሻል ያለመ የዘርፈ ብዙ ባለሙያዎች የአንድ ጤና ጽንሰ-ሀሰብ (Multisectoral One Health) የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል። መድረኩ በብሔራዊ የውሻ አብደት በሽታ ክትትል፣ መከላከልና መቆጣጠሪያ ስትራቴጂ እንዲሁም በክልል አፋጣኝ ምላሽ ሰጪ ቡድን (Regional Rapid Response Team) ምስረታ ላይ ያተኮረ…
Read more

የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ EOC ግምገማ አካሄደ ፡፡

የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ EOC ግምገማ አካሄደ ፡፡ 8/7/18 ዓ/ም ወራቤ ኢንስትቲዩቱ ለህብረተሰቡ የጤና ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ የጤናና ጤና ነክ ክስተቶች ቅኝትና ምላሽ ተግባራት ዙሪያ ሳምንታዊ ግምገማ አካሂዷል። የጤናና ጤና ነክ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ከለላዉ አቻምየለህ የሳምንቱን ሪፖርት ሲያቀርቡ በክልሉ የወባ በሽታን ለመከላከል በየደረጃው…
Read more

በጤናና ጤና ነክ ክስተቶች ቅኝትና ምላሽ ዙሪያ ከመዋቅሮች ጋር በበይነ መረብ ዉይይት ተደረገ

የከምባታ ዞን ጤና መምሪያ የጤናና ጤና ነክ ድን/ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ለህብረተሰቡ ጤና ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ የጤናና ጤና ነክ ክስተቶች ቅኝትና ምላሽ ተግባራት ሳምንታዊ አፈጻጸም ዙሪያ በዞኑ ሥር ካሉ መዋቅሮች የዘርፉ ባለሞያዎች ጋር በበይነመረብ በዛሬው ዕለት የጋራ ዉይይት አካሂዷል፡፡ በዉይይቱም በዋናነት ቀደም ሲል ባሉት ሳምንታት በዞኑ የወባ ሥርጭት ጫና በጨመረባቸዉ መዋቅሮች በወባ በሽታ የተያዙ…
Read more

በክልሉ የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ የአሰጣጥ ስርዓትን በማዘመን ህብረተሰቡን ከጤና ስጋት ለመጠበቅ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ከዞኖች ለተዉጣጡ የጤና ጣቢያ የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ ባለሙያዎች በመሰረታዊ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ ዙሪያ ሲሰጥ የነበረዉ የሆሳዕና ማዕከል ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ለገሰ ጴጥሮስ በማጠቃለያዉ እንደተናገሩት ማህበረሰቡን ከየትኛዉም የተፈጥሮና ሰዉ ሰራሽ የጤና ስጋት ለመጠበቅ ዉጤታማ ስራ…
Read more

በአፍሪካ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎትን በዲጂታል ለማዘመን የሚያስችል አህጉር አቀፍ ወርክሾፕ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የጤና ስርዓትን ለማዘመን እና ጥራት ያለው አገልግሎትን ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ወሳኝ መሣሪያ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በፕሮግራሙ መክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል። ይህንን አህጉራዊ ራዕይ ከግብ ለማድረስ፣ የአፍሪካ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል (Africa CDC) ከቴክኒክ ቡድኖች እና አጋር አካላት ጋር በመሆን ያዘጋጀው “የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎት ዲጂታላይዜሽን ማዕቀፍ (PHC Digitalization Framework)” ረቂቅ ሰነድ…
Read more

የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ መደበኛ EOC ግምገማ አካሄደ ፡፡

የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጤናና ጤና ነክ አደጋዎች ቅኝት ምላሽ ዳይሬክቶሬት ሳምንታዊ የቅኝት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል ፡፡ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን እንደተናገሩት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚፈጠረዉን የወባ በሽታ ለመግታት ጫናዉ የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎችን በመለየት መከላከልን መሠረት ያደረገ የክትትል እና የቁጥጥር ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። ለህብረተሰቡ የወባ…
Read more

ጤና ሚኒስቴር ትብብርን ለማጠናከር እና ቅድሚያ ለሚሰጣቸው የጤና ጉዳዮች እና የጤና ዘርፍ ልማት እና የኢንቨስትመንት ዕቅድ (HSDIP II) ግቦችን ለማሳወቅ ከልማት አጋሮች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተድርገዋል።

ሃገራዊ የጤና ዘርፍ ወቅታዊ ሁኔታዎችን ለአጋሮች የገለጹት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ወቅታዊ አለም አቀፍ ክስተቶችን ተከትሎ ሊያጋጥሙ የሚችሉ መስተጓጎሎችን ለመቋቋም የሚያስችሉ የመፍትሄ ሀሳቦችን ጨምሮ ትኩረት ሊያገኙ የሚገቡ የጤና ጉዳዮችን አስረድተዋል። ሚኒስትሯ በሚቀጥሉት ዓመታት የኢትዮጵያን የጤና ዘርፍ ለመምራት የተነደፈውን የHSDIP II አላማዎችን እና ስትራቴጂካዊ ግቦችን ዘርዝረዋል። ዕቅዱ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ፍትሃዊ ተደራሽነትን ማስፋፋት፣ የጤና…
Read more

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወረርሽኝ ቁጥጥር ስራ ውጤት እያመጣ መሆኑ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳወቀ ።

በክልሉ ለሚገኙ ጤና ጣቢያ የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ ባለሙያዎች መሰረታዊ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ ስልጠና በወራቤ መስጠት ተጀመረ ፡፡ ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን በክልሉ የወረርሽኝ ቁጥጥር ስራዎች ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡ በጤና ተቋም ያሉ የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት እና ምላሽ ባለሙያ የወረርሽኝ ቁጥጥር ስራን በጤና ተቋም…
Read more

በክልሉ በጤና ተቋማት የወሊድ አገልግሎትን 89 % በማድረስ የእናቶችና ህፃናትን ሞት መቀነስ ተችሏል:- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

ቢሮው በጤናውን ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን በወልቂጤ ከተማ ገምግሟል። የቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንዳሉት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ የማህበረሰቡን ተሳትፎ ማጠናከር ወሳኝ በመሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለጤና ተቋማት ግብዓት የሟሟላት ስራ መሠራቱንና ከመንግስት ድጋፍ በተጨማሪ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የግንባታና ግብዓት የሟሟላት ስራ በየአካባቢው እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የመድሀኒት…
Read more