Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Month: May 2026

CERPHI

በድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ አሰጣጥ ላይ የተጀመሩ ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ

(ሆሳዕና፣ሚያዚያ 28/2018):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች የአደጋ ማስመሰል ምላሽ አሰጣጥ ተግባራዊ ልምምድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ ተካሂዷል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወልደሰንበት ሸዋለም እንደገለጹት በድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ አሰጣጥ ላይ የተጀመሩ ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው…
Read more

የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ዝግጁነት, ቅኝትና ምላሽ ስራዎችን በማህበረሰብ ደረጃ ለመተግበር የሚያስችል Community PHEM የተሰኘው ኢኒሸቲቭ ላይ ምክክር ተካሄደ

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የCommunity PHEM ኢኒሸቲቭን በማህበተሰብ ደረጃ ለማስፈጸም የሚያስችል የምክክር ውይይት አካሄደ። ውይይቱ ከክልል ጤና ቢሮ የጤና ኤክስቴንሽን አስተባባሪዎች፣ ከክልል የሕብረተሰብ ጤና አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ሀላፊዎች እና የጤና ትምህርት እና ተግባቦት ባለሙያዎች ጋር የተካሄደ ሲሆን በማህበረሰብ ደረጃ የድንገተኛ ጤና አደጋ ዝግጁነት እና ምላሽ አቅም ማጠናከር ላይ ትኩረት አድርጓል። የኢንስቲትዩቱ…
Read more

የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት ትልልቅ ውጤቶችን ማስመዝገብና ትላልቅ ድሎችን ማጎናጸፍ ችሏል:- ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ

ወራቤ፣ ሚያዚያ 24/2018 (ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን) የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት ትልልቅ ውጤቶችን ማስመዝገብና ትላልቅ ድሎችን ማጎናጸፍ መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ። በላንፉሮ ወረዳ በመንግስት ወጪና በአጋር አካላት እገዛ የተከናወኑ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶች በተመረቁበት መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ወ/ሮ ፋጤ…
Read more

በላንፉሮ ወረዳ የወረዳውን የጤና ተደራሽነት ለማረጋገጥ በወረዳው መንግስት ከ 35 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የወንቴ ሎላ ጤና ጣቢያ በይፋ ተመረቀ!

ወራቤ፣ ሚያዚያ 24/2018 (ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን) በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ የወረዳውን የጤና ተደራሽነት ለማረጋገጥና የማህበረሰቡን የጤና አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ በወንቴ ሎላ ቀበሌ ከ 35 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የወንቴ ሎላ ጤና ጣቢያ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። በመርሃ ግብሩ ላይ የጦራ ከተማ አስተዳደር ከ 3…
Read more

ጠንካራ የጤና ስርዓትን ለመገንባት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አሃድን ማጠናከር አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው

ሪዞልቭ ቱ ሴቭ ላይቭስ የተሰኘው ድርጅት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ተቋማት ወረርሽኝን የመከላከል አቅማቸውን ለማሳደግ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ሲያካሂድ የነበረውን የሙከራ ትግበራ አጠናቆ አስረክቧ። ​የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አሃድን (Primary Care) ማጠናከር በልዩ ትኩረት እየተሰራባቸው ካሉ አምስት ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች መካከል ዋነኛው መሆኑን የጤና ሚኒስትር ድዔታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ገልፀዋል። የማይበገር የጤና ሥርዓት መገንባት የሚቻለው የጤና ተቋማት…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ለዞኖችና ልዩ ወረዳዎች 100 ሚሊዮን የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ።

ድጋፉም፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ከክልሉ መንግስት ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴርና ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በግዢ እና በድጋፍ የተደረገ መሆኑ ተመላክቷል ፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት ባለፉት አመታት የጤናውን ዘርፍ ለማዘመን መጠነ-ሰፊ ሥራዎች ተሰርቷል። በዚህም በጤናው ዘርፍ የመጡ ውጤቶችን ለማስቀጠል የተደረገው ድጋፍ አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ለታለመለት ዓላማ ልውል እንደሚገባ አሳስበዋል አቶ…
Read more

የክትባት ፕሮግራም እና በክትባት የምንከላከላቸው በሽታዎች ቅኝትና ምላሽ ላይ ያተኮረ ግምገማ ተጀመረ

በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና በጤና ሚኒስቴር አዘጋጅነት የክትባት ፕሮግራም እና በክትባት የምንከላከላቸው በሽታዎች ቅኝትና ምላሽ ላይ ያተኮረ የዘጠኝ ወር የጋራ አፈፃፀም ግምግማ መድረክ መካሄድ ጀመረ። የግምገማ መድረኩ ሲጀመር የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከአርባ አመታት በላይ ጠንካራ የክትባት ፕሮግራም እንደነበራት አስታውሰው፤ በግዜው ስድስት የክትባት አይነቶች ፕሮግራሙ የተጀመረ ሲሆን አሁን ላይ…
Read more

የአርማወር ሐንስን የምርምር ኢንስቲትዩት እየተገነባ ላለው የጤና ሥርዓት እና የምርምር ሥነ-ምህዳር ከፍተኛ ሚና አለው – የጤና ሚኒሰትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ

የአርማወር ሐንስን የምርምር ኢንስቲትዩት ከዓለም አቀፍ ደረጃዎች ጋር የተጣጣሙና ለአገራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በቀጥታ ምላሽ የሚሰጡ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ሳይንሳዊ ሥራዎችን ለመደገፍ ተብሎ የተገነባ መሆኑን የጤና ሚኒሰትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ አገራዊ ፖሊሲዎችን እና የሕክምና ልምዶችን የሚደግፉ መረጃዎችን በማመንጨት ረገድ የጤና ምርምር ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ በአገር ውስጥ…
Read more

የኢትዮጵያ 16ኛው የወባ ጥናትና ምርምር ኔትወርክ(Ethiopian Malaria Research Network: EMRN) ሳይንቲፋክ ሲምፖዚየም በድሬዳዋ ከተማ በድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር፣ ከድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ እና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 16ኛው የኢትዮጵያ የወባ ጥናትና ምርምር ኔትወርክ (EMRN) ሳይንሳዊ ሲምፖዚየም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በድምቀት ተካሂዷል። “በአገር ውስጥ ሀብት ማሰባሰብን በማካተት እና በአዲስ ሳይንሳዊ ፈጠራዎችን በማጠናከር የወባ ቁጥጥርንና ማጥፋትን ማጠናከር እና ማሻሻል” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ…
Read more

የጤና ሚኒስቴር በፌዴራል ሆስፒታሎች የስራ አፈጻጸምና የጤና ባለሙያዎችን ማበረታቻ ዙሪያ የምክክር መድረክ አካሄደ

የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር እና የጤና ባለሙያዎችን ደህንነትን ለማሻሻል የታለሙ ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ከፌዴራል ሆስፒታሎች አመራሮች ጋር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ደ/ር ደረጀ ዱጉማ በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል። ውይይቱ በዋናነት ያተኮረባቸው ጉዳዮች የሆስፒታሎች የትርፍ ሰዓት ክፍያ (Duty Payment) መመሪያ አፈጻጸም ሁኔታ፣ የግል ህክምና (Private Wing Service) አገልግሎት ማስፋፋት፣ የሰራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የካፊቴሪያ እና የተረኛ ባለሙያዎች…
Read more