Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

የአፍሪካን የወደፊት እጣ ፈንታ ለመወሰን በሴቶች፣ ህጻናት እና ወጣቶች ጤና ላይ ኢንቨስት ማድረግ ያስፈልጋል::

ከ39ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን በሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጤና ዙሪያ ከፍተኛ የሚኒስትሮች እና አጋሮች ውይይት ተካሄደ። ​የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን በተካሄደው የሚኒስትሮች እና አጋሮች ውይይት ተገኝተው ባስተላለፉት መልልዕክት፣ የአፍሪካን የወደፊት እጣ ፈንታ ለመወሰን በሴቶች፣ህጻናት እና ወጣቶች ጤና ላይ ኢንቨስት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። አፍሪካ የአለማችን ብዙ ወጣት…
Read more

ከጥቃቅን ንጥረ ምግቦች (multiple micronutrient supplementation) የሚዘጋጀ እንክብል በእርግዝና ወቅት ለነፍሰጡር እናቶች መስጠት ጠቃሚ ነው!

የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን እንዲሁም ከሁሉም ክልሎች፣ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በጥናትና በሙከራ ደረጃ በተወሰኑ ክልሎች ለነፍሰጡር እናቶች ሲሰጥ የነበረው የMMS (multiple micronutrient supplementation) ወደ ሌሎች ክልሎችና ወረዳዎች የማስፋፊያና ማስተግበሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል። በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ ባስተላለፉት መልዕክት ለነፍሰጡር እናቶች…
Read more

ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ የጤና ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የጎንዮሸ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል።

“የአፍሪካን የጤና ደህንነት እና የሉዓላዊነት አጀንዳ ማራመድ፡ ቁርጠኛ ፋይናንስ እና አመራርን በመጠቀም ዘላቂነትን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ቃል የአፍሪካን የጤና ስርዓቶች በዘላቂ ፋይናንስ፣ ጠንካራ አመራር እና በራስ መተማመንን ለማረጋገጥ በተሻለ አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያተኮረ የጎንዪሽ ስብሰባ በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) እየተካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢፌድሪ የጤና ሚኒስትር እና…
Read more

የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ስርዓትና የመረጃ ልውውጥ ሂደትን በማጠናከር በማህበረሰቡ ላይ የሚከሰተውን ወረርሽኝ በቅንጅት መከላከል እንደሚገባ የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት አስታወቀ::

(ሆሳዕና፦ የካቲት 6 /2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት በህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ላይ በተከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀላባ ቁሊቶ ከተማ መክሯል። የክልሉ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን እንደገለፁት የክልሉ ጤና ኢኒስቲትዩት በህብረተሰቡ ጤና አጠባበቅ ላይ በርካታ ስራዎችን አከናውኗል እያከናወነም ይገኛል ብለዋል። የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ጠንካራ የላብራቶሪ ምርመራ አገልግሎቶች፣…
Read more

የክልሉን ህብረተሰብ ከተየያዩ የጤና ስጋቶች ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን መድረኩን በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት ማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ እንደ ክልል በሕብረተሰብ ጤና ዙሪያ በተተገበሩ ተግባራት ኢንስቲትዩቱ ያስቀመጣቸው ራዕይ፣ ተልዕኮ እና ግቦች ለመፈጸም በቁርጠኝነት…
Read more

“የስርዓተ-ምግብ ፕሮግራሞች ተጽዕኖን በማሳደግ ለመምራት እና ለማፋጠን ተጨባጭ እና አስተማማኝ መረጃ ማመንጨት አስፈላጊ ነው” የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከኑትሪሽን ኢንተርናሽናል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጆኤል ስፔንሰር ጋር በኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራሞችን ለማጠናከር እና የዘርፈ ብዙ ትብብርን ለማሳደግ ተወያይተዋል። በውይይታቸው ዶ/ር መቅደስ በስርዓተ-ምግብ ፕሮግራሞች ተጽዕኖን በማሳደግ ለመምራት እና ለማፋጠን ተጨባጭ እና አስተማማኝ መረጃ ማመንጨት አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል። የስርዓተ ምግብ መዛባት ችግርን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመፍታት እና ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰቦች…
Read more

የሞለኪውላር ክትትል ተነሳሽነት ወባን በተሻለ ሁኔታ ለመዋጋት ጥቅም ላይ የሚውል ተጨባጭ ማስረጃዎችን አስገኝቷል::

የአፍሪካ ቀንድ የወባ ሞለኪውላር ክትትል ዓመታዊ የግምገማ ስብሰባ ተካሂዷል፣ በስብሰባው ከተለያዩ ሃገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶችን እና አጋሮችን በማሰባሰብ የምርምር ግኝቶችን ገምግሟል። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንዳሉት የሞለኪውላር ክትትል ተነሳሽነት ወባን በተሻለ ሁኔታ ለመዋጋት ጥቅም ላይ የሚውል ተጨባጭ ማስረጃዎችን አስገኝቷል። በአመቱ በአንዳንድ አገሮች የወባ በሽታ የጨመረ ቢሆንም፣ በተሰራዉ የተቀናጀ ስራ ዉጤትም መገኘቱን ተናግረዋል። ዶ/ር መቅደስ የወባ…
Read more

በክልሉ የእናቶች ጤናን ለማሻሻል ውጤታማ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ ፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል የጤናማ እናትነት ወር በቡታጅራ ጠቅላላ ሆስፒታል እየተከበረ ይገኛል ። የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የእለቱን ፕሮግራም ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የጤናማ እናትነት ወርን ለእናቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በላቀ ደረጃ ተደራሽ በማድረግ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ የሚሰራበት መሆኑን ተናግረዋል ።…
Read more

እናስተዋውቅዎ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሾሙት ግርማው አበበ (ዶ/ር) ማን ናቸው?

በመንግስታቱ ድርጅት የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ተመራማሪዎች አስተባባሪ ሆነው ግርማው አበበ (ዶ/ር) ተሹመዋል። ለመሆኑ ግርማው አበበ ማን ናቸው? ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለመተግበር በምትታትር ሀገር ውስጥ እንደዚህ አይነት በዘርፉ ባለምጡቅ አዕምሮ ኢትዮጵያዊ ማግኝትና በመንግስታቱ ድርጅት ስር የሚገኘውን ዓለም ዓቀፍ ተቋም መምራት የሚኖረው ሚና ቀላል አይደለም ። ከኒውክለር የጦር መሳሪያ በላይ እጅግ አስፈሪ በሆነው…
Read more

በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ ጥራት መስፈርቶች ላይ ለጤና ተቋማት የበላይ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ::

በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ የጥራት መስፈርቶች (ISO 15189፡2022 Standards) ትግበራ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ጥር 28/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሥልጠና ማእከል በተሳካ ሁኔታ ተሰጥቷል:: በዚህም መድረክ በISO 15189፡2022 መስፈርቶች አክሬዲቴሽን እና በSLMTA የትግበራ መርሃ-ግብሮች ላይ እየተሳተፉ ካሉ የተለያዩ ጤና ተቋማት የተጋበዙ የበላይ ኃላፊዎችና ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ…
Read more