Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከታዝማ የውስጥ ደዌና የቀዶ ህክምና ልዩ ማዕከል ጋር በመተባበር ነፃ የልብ ቀዶ ህክምና መስጠት ጀመረ

ታዝማ ሜዲካል እና ሰርጂካል እስፔሻላይዝድ ማዕከል 11 ለሚሆኑ የልብ ሁሙማን ህፃናት ከሚያዝያ 13 እስከ 18 2018 ዓ/ም ወራቤ ኮምፕረሄንሲቪ ፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዉስጥ የልብ ቀዶ ህክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት የልብ ቀዶ ህክምና ዘመቻው በዘርፉ ያለውን የወጪ ጫና እና ህክምናውን ለማግኘት የሚደረገውን እንግልት ከማቃለል ረገድ ሚናዉ…
Read more

የጤና ሚኒስቴር የህብረተስብ ጤና አደጋዎችና በሽታዎች አስቀድሞ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ከአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) ጋር የትብብር ስራውን አጠናክሮ መቀጠል በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ዉይይት አድርገዋል

በውይይቱ ወቅት፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከCDC ጋር ለረጅም ጊዜ የተገነባው ትብብር በጤና ስርአት ማጠናከር፣ በኤች አይ ቪ ኤድስና በወባ ፕሮግራሞች እንዲሁም በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዘርፍ ያስመዘገበውን ግልጽ ውጤት በማስታወስ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። በቀጣይም ይህ ትብብር በተለይ በድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነት እና ምላሽ አሰጣጥ ስርዓትን ማጠናከር እንዲሁም በክትባት አገልግሎት እና በመረጃ ስርዓት ማዘመን ዘርፎች ላይ…
Read more

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ገመገመ::

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ስትራቴጂካዊ እና ኦፕሬሽናል ዕቅድ አፈጻጸምን የክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀላፊዎች እና የኢንስቲትዩቱ አመራሮች በተገኙበት የሚገመግም የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ከተማ አካሄደ። የግምገማ መድረኩ ዋና ዓላማ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር፣ በላቦራቶሪ አቅም ግንባታና አገልግሎት በጥናትና ምርምር ፣ በብሔራዊ የጤና መረጃ ዙሪያ እንዲሁም በአለም አቀፍ ጤና ደንብና…
Read more

የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት አዲሱ ዘመናዊ የጤና ምርምር ላቦራቶሪ ኮምፕሌክስ ተጎበኘ

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመረቀውና በዓይነቱ ልዩ የሆነው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) አዲሱ ላቦራቶሪ ኮምፕሌክስ በሠራተኞችና በእንግዶች ተጎበኘ። የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕ/ር አፈወርቅ ካሱ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ከ20 ሠራተኞች ተነስቶ ዛሬ ከ700 በላይ ባለሙያዎችን የያዘ ግዙፍ የሳይንስ ማዕከል ሆኗል። ማዕከሉ ሀገር በቀል እውቀትን ወደ ላቀ ሳይንሳዊ ምርምር በማሸጋገር የሀገራችንን የጤና ደኅንነት…
Read more

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ስታርሊንክን በመጠቀም በገጠር የጤና ተቋማት የኢንተርኔት አገልግሎትን ለማስፋት የሚያስችል ውይይት ከስፔስኤክስ ልዑካን ቡድን ጋር አካሂደዋል።

በስብሰባው የስፔስኤክስ ልዑካን ቡድን ስታርሊንክ በአሁኑ ጊዜ በ169 አገሮች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን እና በኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎት ለመጀመር ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል። አገልግሎቱ በተለይም በሩቅ እና በቂ የኔትወርክ አገልግሎት በማያገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት ግንኙነት ለማቅረብ ያለመ ነው። ስፔስኤክስ በተለይ ለገጠር የጤና ተቋማት የኢንተኔት አገልግሎትን በማቅረብ ረገድ መልካም አማራጭ ማቅረቡን የገለጹት ዶ/ር መቅደስ፣ በአገሪቱ ውስጥ…
Read more

በጤና ዘርፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) አጠቃቀምን ለማሳደግ የሚረዳ ውይይት ተካሄደ

በጤና ዘርፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) አጠቃቀምን ለማሳደግ የሚረዳ ውይይት ተካሄደ __________ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከጌትስ ፋውንዴሽን ልዑካን ቡድን ጋር በጤና ዘርፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዙ የምርመራ መሳሪያዎችን ወደ ተግባር ለማስገባት ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰራ የገለጹት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣…
Read more

አርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ውስጥ የተገነባው አዲሱ ዘመናዊ የምርምር ሕንፃ እና ፋይዳዎቹ:-

– 34 ዘመናዊ ላቦራቶሪዎች – የላቁ የጄኖሚክስ (genomics) እና የባዮኢንፎርማቲክስ (bioinformatics) መሠረተ ልማቶች፣ – የባዮኢኩዊቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን አካቷል። ‎ ተቋሙ ለሥልጠና እና ለምርምር የተመደቡ ቦታዎችን የያዘ ሲሆን በኢትዮጵያ እና በመላው አፍሪካ ለሳይንስ ሥነ ምሕዳር መስፋፋትና አቅም ግንባታ አዲስ መለኪያ አስቀምጧል። The state-of-the-art research complex at the Armauer Hansen Research Institute (AHRI) and its contributions: –…
Read more

የፓርኪንሰን በሽታ የአንጎላ ነርቭ ስርዓትን የሚጎዳና ቀስ በቀስ የሚጨምር ነው!

በዓለም አቀፍ ደረጃ መጋቢት 24 በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች የሚከበረው የፓርኪንሰን በሽታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን የጤና ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የፓርኪንሰን ፔሽንትን ሰፓርት ኦርጋናይዜሽን ኢትዮጵያ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና የማህበሩ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ተከብሯል። በግንዛቤ ማስጨበጫው መድረክ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ዶ/ር ህይወት ሰለሞን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ…
Read more

የሮተሪ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ፖሊዮን እንደ ሀገር ለማጥፋት የሚታደረገዉን ጥረት እንደሚያግዝ ገለጸ

የሮተሪ ኢንተርናሽናል የዲስትሪክት 1710 የፖሊዮ ፕላስ (PolioPlus) ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርጓል። በሮታሪያን ዣን ፒሮን (Jean Piron) የተመራው ይህ ልዑክ፣ በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ እና በምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር መልካሙ አብቴ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። በውይይቱ ወቅት ዶ/ር መሳይ ኃይሉ፣ ኢትዮጵያ የፖሊዮ በሽታን ከሀገር ለማጥፋት…
Read more

ታካሚ ላይ በማተኮር እና የማህበረሰብ ተሳትፎን በማሳደግ፣ የቲቢን በሽታን ለመከላከል መስራት እንደሚገባ ተገለጸ ፡፡

የኢትዮጵያ የቲቢ ምርምር አማካሪ ምክር ቤት የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ እና 20ኛውን ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ኮንፈረንስ ” ቲቢን ማጥፋት እንችላለን!” በሚል መሪ ቃል በድምቀት እየተካሄደ ነው። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ለቲቢ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ጠንካራ የአመራር ቁርጠኝነት እና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል ። የኢትዮጵያ የቲቢ…
Read more