Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

የክልሉን ህብረተሰብ ከተየያዩ የጤና ስጋቶች ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን መድረኩን በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት ማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ እንደ ክልል በሕብረተሰብ ጤና ዙሪያ በተተገበሩ ተግባራት ኢንስቲትዩቱ ያስቀመጣቸው ራዕይ፣ ተልዕኮ እና ግቦች ለመፈጸም በቁርጠኝነት…
Read more

“የስርዓተ-ምግብ ፕሮግራሞች ተጽዕኖን በማሳደግ ለመምራት እና ለማፋጠን ተጨባጭ እና አስተማማኝ መረጃ ማመንጨት አስፈላጊ ነው” የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከኑትሪሽን ኢንተርናሽናል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጆኤል ስፔንሰር ጋር በኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራሞችን ለማጠናከር እና የዘርፈ ብዙ ትብብርን ለማሳደግ ተወያይተዋል። በውይይታቸው ዶ/ር መቅደስ በስርዓተ-ምግብ ፕሮግራሞች ተጽዕኖን በማሳደግ ለመምራት እና ለማፋጠን ተጨባጭ እና አስተማማኝ መረጃ ማመንጨት አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል። የስርዓተ ምግብ መዛባት ችግርን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመፍታት እና ተጋላጭ ለሆኑ ማህበረሰቦች…
Read more

የሞለኪውላር ክትትል ተነሳሽነት ወባን በተሻለ ሁኔታ ለመዋጋት ጥቅም ላይ የሚውል ተጨባጭ ማስረጃዎችን አስገኝቷል::

የአፍሪካ ቀንድ የወባ ሞለኪውላር ክትትል ዓመታዊ የግምገማ ስብሰባ ተካሂዷል፣ በስብሰባው ከተለያዩ ሃገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶችን እና አጋሮችን በማሰባሰብ የምርምር ግኝቶችን ገምግሟል። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንዳሉት የሞለኪውላር ክትትል ተነሳሽነት ወባን በተሻለ ሁኔታ ለመዋጋት ጥቅም ላይ የሚውል ተጨባጭ ማስረጃዎችን አስገኝቷል። በአመቱ በአንዳንድ አገሮች የወባ በሽታ የጨመረ ቢሆንም፣ በተሰራዉ የተቀናጀ ስራ ዉጤትም መገኘቱን ተናግረዋል። ዶ/ር መቅደስ የወባ…
Read more

በክልሉ የእናቶች ጤናን ለማሻሻል ውጤታማ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ ፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል የጤናማ እናትነት ወር በቡታጅራ ጠቅላላ ሆስፒታል እየተከበረ ይገኛል ። የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የእለቱን ፕሮግራም ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የጤናማ እናትነት ወርን ለእናቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በላቀ ደረጃ ተደራሽ በማድረግ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ የሚሰራበት መሆኑን ተናግረዋል ።…
Read more

እናስተዋውቅዎ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሾሙት ግርማው አበበ (ዶ/ር) ማን ናቸው?

በመንግስታቱ ድርጅት የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ተመራማሪዎች አስተባባሪ ሆነው ግርማው አበበ (ዶ/ር) ተሹመዋል። ለመሆኑ ግርማው አበበ ማን ናቸው? ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ለመተግበር በምትታትር ሀገር ውስጥ እንደዚህ አይነት በዘርፉ ባለምጡቅ አዕምሮ ኢትዮጵያዊ ማግኝትና በመንግስታቱ ድርጅት ስር የሚገኘውን ዓለም ዓቀፍ ተቋም መምራት የሚኖረው ሚና ቀላል አይደለም ። ከኒውክለር የጦር መሳሪያ በላይ እጅግ አስፈሪ በሆነው…
Read more

በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ ጥራት መስፈርቶች ላይ ለጤና ተቋማት የበላይ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ::

በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ የጥራት መስፈርቶች (ISO 15189፡2022 Standards) ትግበራ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ጥር 28/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሥልጠና ማእከል በተሳካ ሁኔታ ተሰጥቷል:: በዚህም መድረክ በISO 15189፡2022 መስፈርቶች አክሬዲቴሽን እና በSLMTA የትግበራ መርሃ-ግብሮች ላይ እየተሳተፉ ካሉ የተለያዩ ጤና ተቋማት የተጋበዙ የበላይ ኃላፊዎችና ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ…
Read more

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን በነቀምቴና አካባቢው የሚገኙ ጤና ተቋማትን ጎብኝተዋል።

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ቡድን በነቀምቴና አካባቢው የሚገኙ ጤና ተቋማትን ጎብኝተዋል። ___________ ይህ ጉብኝት ኅብረተሰቡ እያገኘ ያለውን የጤና አገልግሎት ጥራትና የተቋማቱን አጠቃላይ ቁመና በአካል ተገኝቶ ለመገምገም ታላቅ ፋይዳ ያለው ሲሆን፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየትና ተግዳሮቶችን በቅርበት በመረዳት ምላሽ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ​ልዑካን ቡድኑ በቆይታው የዞኑን መድኃኒት አቅራቢ…
Read more

የጤና ተቋማትን የሕክምና ግብዓት ለማሟላት ተጨማሪ አቅም የሆነው ፕሮጀክት።

የጤና ተቋማትን የሕክምና ግብዓት ለማሟላት ተደማሪ አቅም የሆነው ፕሮጀክት ****************** በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሕክምና መሣሪያዎች አቅርቦት ፕሮጀክት ምዕራፍ ሁለት ማስፈጸሚያ የሚውል የብድር ስምምነት ረቂቅ አዋጅ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር የአስረጂ መድረክ አካሂዷል፡፡ በመድረኩ የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ መንግሥታት በጤናው ዘርፍ ያለውን የመሠረተ ልማት እጥረት ለመቅረፍ በማለም የተፈራረሙት የ30…
Read more

በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን የጤና ተቋማትንና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ለመጎብኘት ነቀምቴ ከተማ ገብቷል።

በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን የጤና ተቋማትንና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ለመጎብኘት ነቀምቴ ከተማ ገብቷል። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና ሌሎች የመንግስትና አጋር ድርጅቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ነቀምቴ ከተማ የገቡ ሲሆን በቆይታቸዉም ከጤና መሠረተ ልማት አቅርቦት ጀምሮ እየተከናወኑ…
Read more

የሆሳዕና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ28ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 34 የጤና ተማሪዎችን አስመረቀ።

(ሆሳዕና፣ ጥር 23/2018 ዐ/ም) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሆሳዕና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በደረጃ 4 እና በዲግሪ ፕሮግራም በተለያዩ መርሃ-ግብሮች ለ28ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 34 የጤና ተማሪዎች አስመርቋል። የዕለቱ የክብር እንግዳና የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደተናገሩት የክልሉ መንግሥት በጤናው ሴክተር ለማሳካት ካስቀመጣቸው የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅዶች አመርቂ ውጤት ተገኝቷል። በቤተሰብ ደረጃ የበለጸገ…
Read more