የክልሉን ህብረተሰብ ከተየያዩ የጤና ስጋቶች ለመከላከል የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለጸ ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን መድረኩን በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት ማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ እንደ ክልል በሕብረተሰብ ጤና ዙሪያ በተተገበሩ ተግባራት ኢንስቲትዩቱ ያስቀመጣቸው ራዕይ፣ ተልዕኮ እና ግቦች ለመፈጸም በቁርጠኝነት…
Read more
