Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

ብራዚል – ሳኦፖሎ ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአለም አቀፉ መድረክ!

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ የሆስፒታሉን ‘የታካሚ ደህንነት አጠባበቅ ሂደት እና የተገኘውን ለውጥ’ በአለም የጤና ድርጅት 41ኛው አለም አቀፍ የጤና እንክብካቤ ዘርፍ የጥራት ዓለም አቀፍ ማኅበር (ISQua) ጉባኤ ላይ አቅርበዋል። ዋና ስራ አስኪያጁ በአለም አቀፉ ፕሮግራም ተገኝተው የተቋሙን ‘የታካሚ ደህንነት አጠባበቅ ሂደት እና የተገኘውን ለውጥ’ በማካፈላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው ለዚህም…
Read more

የአፍሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠርያ ማዕከል የመድሃኒት እና የህክምና መሣሪያዎች አቅርቦት ለአፍሪካ ሃገራት ለመጀመር የሚረዳ አህጉራዊ የውይይት መድረክ ተካሄደ::

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ከአፍሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ጋር በመተባበር በአፍሪካ የተቀናጀ የመድሃኒት እና የህክምና መሣሪያዎች ግዢ እና አቅርቦት ሜካኒዝም ጅምር ላይ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ውይይት አካሂደዋል፡፡ ሜካኒዝሙ አፍሪካ ሲዲሲ በጋራ በሚሰበሰብ ፈንድ የመድኃኒት ምርቶችን እና ክትባቶችን በመግዛት ለአባል ሀገራት ማሰራጨት እና የሃገር ውስጥ ምርትን ለማበረታታት የሚያስችለው ነው። በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር…
Read more

ማህበረሰቡ ፣ባለሀብትና መንግስት በማስተባበር ከ190 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለጤና ተቋማት ግብዐት ማሟላት እንደተቻለም ተገለጸ።

“በባለቤትነት ላይ የተመሰረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ ” በሚል መሪ ቃል የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 ማጠቃለያ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የማህበረሰቡ ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዋነኛው አማራጭ የጤና መድህን አጋግሎት መሆኑ ተገልጿል!! በመድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣የጉራጌ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ…
Read more

በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጤና ጽህፈት ቤት የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

“በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጤና ጽህፈት ቤት የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው። የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ “በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት በ2017 ዓ.ም ዓመታዊ በሙዱላ…
Read more

ከ15 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ሬዝደንት አማካሪዎች ቴክኖሎጂ በትምህርት ስርዓቱ ስለሚካተትበት ሁኔታ እየመከሩ ነው

ከ15 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ሬዝደንት አማካሪዎች በአፍሪካ የህብረተሰብ ጤና ችግሮችን በፍጥነት ለመለየት፣ ለመመርመርና ለማከም እንዲቻል ዘመን ያፈራው ቴክኖሎጂ በትምህርት ስርዓቱ በሚካተትበት ሁኔታ በአዲስ አበባ እየመከሩ ነው። የፊልድ ኢፒዲሞሎጅ ስልጠና ፕሮግራም ለህብረተሰብ ጤና አገልግሎት የጀርባ አጥንት መሆኑን የገለፁት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ ቀጣዩ የአፍሪካ ጤና አገልግሎት በመረጃ ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ የኢፒዲሞሎጅ ባለሙያዎች…
Read more

የቻይና የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ባለስልጣን ከኢንስቲትዩቱ ጋር በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያየ

በዛሬው እለት ከቻይናው የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ባለስልጣን (Chinese Disease Control and Prevention Authority /CDCPA/) የመጡ የልኡካን ቡድን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ሊሰሩባቸው በሚችሉ መስኮች ላይ መክረዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ እንግዶቹን በተቀበሉበት ወቅት ከዚህ ቀደም በሁለቱ ሀገራት ግንኙነቶች የተደረጉ የሰው ሀይል አቅም ግንባታና ስልጠና እንዲሁም የልምድ ልውውጥ ተግባራት አመርቂ ውጤቶች ማስገኘታቸውን…
Read more

12ኛው አመታዊ የ COECSA ኮንግረስ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

“የተርሸሪ የአይን እንክብካቤን በ COECSA ሃገራት ማሳደግ፡ ጊዜው አሁን ነው” በሚል መሪ ቃል 12ኛው የምስራቅ፣ መካከለኛ እና ደቡብ አፍሪካ የዓይን ህክምና ኮሌጅ (COECSA) ኮንግረስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። ኮንግረሱ አህጉራዊ እና አለምአቀፍ ባለሙያዎችን፣ የአይን ጤና ባለሙያዎችን እና ሰልጣኞችን ጨምሮ ከ40 በላይ ከሚሆኑ ሃገራት የተውጣጡ ከ600 በላይ ተሳታፊዎችን በማሰባሰብ በአፍሪካ የአይን ህክምናን ማሳደግ ላይ ምክክር ያደርጋል።…
Read more

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ወር አፈጻጸም እና ሳምንታዊ የEOC ግምገማ ተካሄደ፤

ነሀሴ 15/2017 የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ወር አፈጻጸም እና ሳምንታዊ የEOC ግምገማ በዛሬው እለት ተካሂዷል፡፡ የአፈጻጸም ሪፖርቱ በልማት እቅድ ቡድን መሪ አቶ ሀብታሙ ጽጌ የቀረበ ሲሆን ሳምንታዊ የEOC ሪፖርት በድንገተኛ በሽታዎች አሰሳ እና ቅኝት ቡድን መሪ በሆኑት በአቶ ነስረዲን ኑርዬ አማካኝነት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በግምገማ መድረክ የመምሪያው ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ…
Read more

የወቅቱ አየር ለወባ ወረርሽኝ ክስተት ምቹ በመሆኑ የወባ መከላከል ሥራ ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ

የከምባታ ዞን የድንገተኛ አደጋዎችና ወረርሽኞች መከላከልና ቁጥጥር ግብረሀይል የወባ መከላከልና መቆጣጠር ስራን አስመልክቶ በየደረጃው እየተሠሩ ያሉ ተግባራትን የሚገመግም መድረክ በዱራሜ ከተማ አካሂዷል። በመድረኩም የክረምት ወቅትን ተከትሎ ለወባ ትንኝ መራባት አመቺ የአየር ንብረት ሁኔታ በስፍት የሚታይ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚስተዋለውን የወባ በሽታ ጫናን ለመግታት በወባ መከላከል፣ መቆጣጠር እና ማስወገድ ዙሪያ በዞኑ በሚገኙ መዋቅሮች እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት…
Read more

በበጀት አመቱ ኤች አይቪ ኤድስን የመከላከል እና መቆጣጠር ስራዎች በትኩረት መሰራታቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ ፡፡

የቢሮው የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግመገማ እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ትኩረት ያደረገ የውይይት መድረክ አየተካሄደ ነው ፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃልፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ ባስተላለፉት መልዕክት በበጀት አመቱ ኤች አይቪ ኤድስን የመከላከል እና መቆጣጠር ስራዎች በትኩረት መሰራታቸውን አስረድተዋል። በበጀት ዓመቱ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ…
Read more