
በስብሰባው የስፔስኤክስ ልዑካን ቡድን ስታርሊንክ በአሁኑ ጊዜ በ169 አገሮች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን እና በኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎት ለመጀመር ፍላጎት እንዳለው አብራርተዋል። አገልግሎቱ በተለይም በሩቅ እና በቂ የኔትወርክ አገልግሎት በማያገኙ አካባቢዎች ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት ግንኙነት ለማቅረብ ያለመ ነው።
ስፔስኤክስ በተለይ ለገጠር የጤና ተቋማት የኢንተኔት አገልግሎትን በማቅረብ ረገድ መልካም አማራጭ ማቅረቡን የገለጹት ዶ/ር መቅደስ፣ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ብዙ የጤና ተቋማት አሁንም አስተማማኝ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን እያገኙ አለመሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የአገሪቱን የዲጂታል የጤና ስርዓት ለማጠናከር ከስፔስኤክስ ጋር በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላት ዶ/ር መቅደስ ገልፀዋል።
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
See less



