Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን አስመለክቶ የክልሉ ምክር ቤት ከማህበራዊ ዘርፍ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በጋራ በመቀናጀት ህዝባዊ ውይይት አካሄደ::

CERPHI

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጤና ዘርፍ የተከናወኑ ያሉ ስራዎች በተመለከተ የክልል ምክር ቤት ከማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ጋር በመቀናጀት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ ህዝባዊ ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በውይይት መድረኩም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የምክር ቤቱ ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ መነቴ ሙንዲኖ የምክር ቤቱ ማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግዛቸው ዋሌራ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሽመልስ ዋንጎሮ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና ከባዳዎቾ ወረዳ የመጡ ባለድርሻ አካላት ታድመውበታል።

በክልሉ ጤና ቢሮ የተዘጋጀው የመወያያ ጽሁፍ ቀርቧል።

የእናቶች ጤና አገልግሎት ስራዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽን መቀዛቀዝና ስርዓተ ምግብ እና የተለያዩ ተላላፊ በሽታ ችግሮች በአግባቡ ከመምራት አኳያ ችግሮች እንዳሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የውይይት መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት ተናግረዋል።

በጤና ስርዓቱ ያሉ ችግሮች በአፋጣኝ መፍታት እንደሚገባ ተገልጿል።

ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮች በክልሉ የሚገኘው የጤና ስርዓት መስተካከል የሚገባቸውን ጉዳዮች በመነሳት ላይ ይገኛል።ምንጭ ደሬቴድ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *