Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

የፓርኪንሰን በሽታ የአንጎላ ነርቭ ስርዓትን የሚጎዳና ቀስ በቀስ የሚጨምር ነው!

CERPHI

በዓለም አቀፍ ደረጃ መጋቢት 24 በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች የሚከበረው የፓርኪንሰን በሽታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን የጤና ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የፓርኪንሰን ፔሽንትን ሰፓርት ኦርጋናይዜሽን ኢትዮጵያ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና የማህበሩ አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ተከብሯል።

በግንዛቤ ማስጨበጫው መድረክ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ዶ/ር ህይወት ሰለሞን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ እንዳሉት የፓርኪንሰን በሽታ የአንጎላ ነርቭ ስርዓትን የሚጎዳና ቀስ በቀስ እየጨመረ የሚሄድ በሽታ እንደሆነ አንስተው እጅ ወይም አካል መንቀጥቀጥ፣ የእንቅስቃሴ መዘግየት/መዛል፣ የጡንቻ መጠንከር፣ የሚዛን መዛባት/መውደቅ፣ ድብርት ወይም ጭንቀት፣ የእንቅልፍ ችግር፣ ማሽተት አለመቻል እንዲሁም የድካም ስሜት የበሽታው ምልክቶች መሆናቸውን ገልጸው የበሽታው ምልክቶቹ የሚታይባቸው ስዎች በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

አክለውም በጤና ሚኒስቴር ከፓርኪንሰን በሽታ ተያይዞ በርካታ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ከተሰሩ ስራዎችም መካከል የነርቭ ህመም እና ፓርኪንሰን በሽታ ጨምሮ የህክምና መመሪያ ማዘጋጀትና በጤና ፓሊሲው ውስጥ ትኩረት እንዲሰጠው መደረጉ፣ ለታካሚዎች ተደራሽና ፈጣን ምርመራና ህክምና እንዲያገኙ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረገ እንደሚገኝ፣ የመድኃኒትና የሪሀቢሊቴሽን አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ እንዲሁም በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እየተከናወኑ እንደሚገኝ አብራርተው የታካሚዎችን ችግር ለመቅረፍና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ላለው ለፓርኪንሰን ፔሽንትን ሰፓርት ኦርጋናይዜሽን ኢትዮጵያ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የፓርኪንሰን ፔሸንትን ሰፓርት ኦርጋናይዜሽን ኢትዮጵያ መስራችና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኒውሮሎጂ ሙሁራን ተገኝተው እለቱን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Website: moh.gov.et

Facebook: Ministry of Health,Ethiopia

Twitter: x.com/fmohealth

YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia

Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia

Telegram: t.me/M0H_EThiopia

Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *