
በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን የጤና ተቋማትንና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ለመጎብኘት ነቀምቴ ከተማ ገብቷል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና ሌሎች የመንግስትና አጋር ድርጅቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ነቀምቴ ከተማ የገቡ ሲሆን በቆይታቸዉም ከጤና መሠረተ ልማት አቅርቦት ጀምሮ እየተከናወኑ ያሉ የጤና ስራዎችን እንድሁም ያጋጠሙ ችግሮች በመመልከት የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያረጋግጡ የሥራ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ይሆናል።
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
