Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

ለሶስት ተከታታይ ቀናት የህብረተሰብ ጤና መረጃ አያያዝ እና ትንተና ላይ ያተኮረው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡

ለተከታታይ ሶስት ቀናት በቡታጅራ ከተማ ሲሰጥ የነበረው የStat እና R ሶፍትዌር ስልጠና መጠናቀቁን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህ/ሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቋል በስልጠናው ላይ የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምርምር ተቋም ባለሙያዎች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከጤና ቢሮ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሉ ዩንቨርስቲዎች፣ ኮሌጅዎች ፣ ከዞን እና ልዩ ወረዳ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ተሳታፊዎቹ ከስልጠና መጨረሻ ላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ ውጤታማነት መረባረብ እንደሚገባ ገለጸ።

(ሆሳዕና ፡ሰኔ 26/2017 )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቡታጅራ ከተማ ያዘጋጀው የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ የንቅናቄ መድረክ ተጠናቋል። የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ ውጤታማነት የሚያግዙ ሁለት ሰነዶች በማጠቃለያ መድረኩ ላይ ቀርበዋል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራሞች ሃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ መድረኩን ሲያጠቃልሉ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃድ ውጤታማነት…
Read more

የእናቶችና ህጻናት ሞትና የሞት መንስኤዎችን አስመልከክቶ የናሙና ምዝገባ ሥርዓት የማስጀመሪያ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈረመ::

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል ከክልል ጤና ቢሮዎች እና ከሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ጋር የእናቶችና ህጻናት ሞት እና የሞት መንስኤዎች እንዲሁም አጠቃላይ የበሽታ ሰርጭት የመለየት እና ያሉትን የክትትል ስርዓቶችን ለማጠናከር የናሙና ምዝገባ ስርዓትን (Sample Registration System/SRS/) ለመዘርጋት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን የማስጀመሪያ የዉይይት መድረክም ሰኔ 24/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ hope SBH ከተባለ አጋር ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ ፡

በክልሉ በተፈጥሮ ከመጠን በላይ የፈሳሽ ክምችት እና የነርቭ ዘንግ ክፍተት ተጠቂ የሆኑ ህጻናት ህክምና እና ድጋፍ እንዲያገኙ የሚያስችል ስምምነት መሆኑ ተገልጿል ፡፡ ስምምነቱን በማስመልከት ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በክልሉ በተፈጥሮ የጤና ችግር ያለባቸው ህጻናት ፈጣን ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡ በተለይም በተፈጥሮ የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ…
Read more

ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ – ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ

ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ – ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ (ሆሳዕና፣ ሰኔ 20/2017)፦ በኢትዮጵያ ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተናገሩ። “ኢኖቬሽን ለሁለንተናዊ የጤና ሽፋን” በሚል መሪ ሃሳብ ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሔድ የነበረው አለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ ተጠናቋል። የጤና…
Read more

የምግብ ደህንነትን በማረጋገጥ በአካልና በአእምሮ ላይ የሚያጋጥመንን የጤና እክል መከላከል ይገባል – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ

(ሆሳዕና:- ሰኔ 20/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በክልሉ በሚገኙ የዱቄትና ዱቄት ውጤት አምራቾች ጋር በንጥረ ነገር የበለፀገ ምርት ማምረት የሚያስችል የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው። የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ የምግብ ደህንነትን በማረጋገጥ በአካልና በአእምሮ ላይ የሚያጋጥመንን የጤና እክል…
Read more

ፈጠራን ባሕል በማድረግ የሕክምና ዘርፉን መደገፍ ይገባል

ፈጠራን ባሕል በማድረግ የሕክምና ዘርፉን መደገፍ ይገባል ሲሉ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ ገልጸዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽን እና ጥራት ጉባኤ ዛሬ 2ኛ ቀኑን ይዟል። በጉባኤው ላይ “ፈጠራ ሁሌም ጥራትን ለማምጣት ይረዳል” ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ፈጠራ የታከለበት ስራ የጤና ዘርፉን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል አመላክተዋል። በኢትዮጵያ የጤና ተደራሽነትና ጥራት ላይ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው፤ ጥራት…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ የድጋፍ እና ክትትል ስምሪት ሰጠ ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ የድጋፍ እና ክትትል ስምሪት ሰጠ ፡፡ የ2017 የሁለተኛ ግማሽ ዓመት ማጠቃለያ ድጋፋዊ ክትትል ከ16/10/17 ዓ/ም ጀምሮ ከዞን እና ልዩ ወረዳ ጀምሮ እስከ እስከ ታች ጤና ተቋማት በመውረድ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት የድጋፍ ክትትል ስራ እንደሚሰራ በኦረንቴሽኑ ተገልጿል ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ…
Read more

የወረርሽኝ በሽታዎች ከመከሰታቸው በፊት የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ

(ሆሳዕና፦ሚያዝያ 24/2017)፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት ምላሽ ዳይሬክቶሬት የ2017 የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማና የህብረተሰብ ድንገተኛ ጤና አደጋዎች ቅኝት እና በመረጃ ስርዓት አተገባበር ዙሪያ የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ ተካሂዷል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን እንደገለፁት የክልሉ ጤና ኢኒስቲትዩት በህብረተሰቡ ጤና…
Read more

በእቅድ ዝግጅት ወቅት ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ አሁን ለተገኘው ውጤት በምክንያትነት ተጠቃሽ ነው – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር )

(ሆሳዕና፣ሚያዚያ 23/2017)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በየፓርቲና በመንግስት በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት አስመልክቶ ክልል አቀፍ የአመራር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እንደገለጹት ፈተናዎቻችንን በመገንዘብ ለተሻለ ለውጥ መስራት ይገባል ብለዋል። ጥንካሬን ማስቀጠል እና ጉድለትን መለየት እቅድን ለማሳካት የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። በእቅድ ዝግጅት ወቅት ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ አሁን…
Read more