Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Category: News

CERPHI

ኢትዮጵያ መቀንጨርን ለመከላከል የምግብ ሥርዓት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅታ እየሰራች ነው – የጤና ሚኒስተር

በኢትዮጵያ የመቀንጨር ተጋላጭነትን ለመቀነስ የምግብ ሥርዓት ፍኖተ ካርታ በማስቀመጥ በቁርጠኝነት እየሰራች ነው ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተናገሩ። በኢትዮጵያ የምግብ ሥርዓት ትግበራ ለወጣቶች፣ ለሕፃናት በተለይ ለታዳጊዎች ጉልህ ሚና አለው ያሉት ሚኒስትሯ፤ የተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን በማስተባበር እየተሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ የሰቆጣ ቃልኪዳንን በማስቀመጥ ወደ ተግባር መግባቷን አንስተዋል። ባለፉት አራት ዓመታት መቀንጨርን…
Read more

ሁለተኛዉ የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓተ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ብዙ ጠቀሜታ አለዉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ

ሁለተኛዉ የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓተ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለዉ የገለጹት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በ ጉባዔው ከሌሎች ሀገሮች የምንማርበት እና እኛም ደግሞ ወደ ተግባር የተሸጋገርንበትን መንገድ ለሌሎች የምናሳይበት ነዉ ብለዋል። በፈረንጆቹ 2021 በተደረገው የመጀመሪያው ጉባዔ ላይ ተሳታፊ የነበረችው ኢትዮጵያ፤ የምግብ ሥርዓት ጉዳይን በዕቅድ ውስጥ በማስገባት ልትተገብራቸው ቃል ከገባችባቸው ጉዳዮች መካከል…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከል መርቆ ከፈተ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከል መርቆ ከፈተ። የቢሮው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሆስፒታሉ ተገኝተው የማዕከሉን ሥራ በይፋ አስጀምረዋል። ማኔጅመንቱ በሆስፒታሉ እየተሰጡ የሚገኙ የህክምና አገልግሎቶችን ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ የህብረተሰቡን ጤና ለማሻሻል በተቋሙ የተጀመሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተመልክቷል። የሆስፒታሉ ስራ-አስኪያጅ ዶ/ር ፍቅረ-ጽዮን በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት፦ ሆስፒታሉ ወደ ሥራ ከገባ…
Read more

በጤናው ዘርፍ መሻሻል እንዲመጣ የጥናትና ምርም ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ በወራቤ ከተማ ተካሂዷል። ሐምሌ 8/2017 ሀላባ ቲቪ —————————- በመድረኩ ላይ ለዕለቱ የተዘጋጀ ሰነድና የአፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ምላሽና ማብራሪያውን የሰጡት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙዔል ዳርጌ በክልሉ የወባና ኮሌራ ወረርሽኝን የመቆጣጠር ልምድ እየዳበረ መምጣቱን አስታውሰው…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አመታዊ ጉባኤውን በወራቤ ከተማ እያካሄደ ነው።

(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 8/2017)፤ ኢንስቲትዩቱ በመድረኩ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የበጀት አመቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተወያየ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት አመት አምስት የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት መሠራቱን አንስተዋል። ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋንን ማፍጠን፣ የህብረተሰቡን የጤና ሁኔታን ማሻሻል፣ ህብረተሰቡን ከድንገተኛ አደጋ መጠበቅ፣ የጤና…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ ግንባታው የተጠናቀቀውን ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ መርቆ ስራ አስጀመረ::

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎና በክልሉ መንግስት ገንዘብ ወጪ የተገነባውን የንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ስራ አስጀመረ። ለሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ግንባታው የአካባቢው ህዝብና የክልሉ መንግስት ከ13ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸው ተገልጿል። የጤና ተቋሙን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የብልጽግና መንግስት…
Read more

ለጤናው ዘርፍ ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ይገባል፡-ጤና ሚኒስቴር::

ለጤናው ዘርፍ ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ይገባል፡-ጤና ሚኒስቴር ********** በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ ድጋፎች በመቀነሳቸው፣ ለጤናው ዘርፍ የሚውል ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። በራስ አቅም ለጤናው ዘርፍ ዘላቂ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ የሚመክር ዓውደጥናት ተካሂዷል። በመድረኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ ድጋፎች መቀነሳቸውን ያነሱት የጤና ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ፤ ለዚህ…
Read more

የቴክኖሎጂ አሰራር ስርዓትን በመከተል ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ተጋላጭነት ስጋትን ለማስቀረት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ ፡፡

ሶስተኛው ዙር የክልሉ ጤና ቢሮ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የ2018 በጀት ዓመት የድንገተኛ ጤና አደጋዎች የተጋላጭነት ስጋት ልየታ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለሀዲያ ዞን ሁሉም ወረዳዎች ለተውጣጡ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች አስተዳደር አስተባባሪዎች ስልጠና በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ለገሰ ጴጥሮ ባስተላለፉት መልዕክት በቴክኖሎጂ የታገዘ የህብረተሰብ…
Read more

በተቀናጀ ጤና ዘመቻ በተሰሩ ሥራዎች የሚታይ ለውጥ መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በበጀት ዓመቱ በተቀናጀ ዘመቻ የተከናወኑ ተግባሮች ግምገማና እውቅና የመስጠት መድረክ በሆሳዕና ከተማ አካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንዳሉት፦ በተቀናጀ ጤና ዘመቻ በተሰሩ ሥራዎች የሚታይ ለውጥ ተመዝግቧል። አቶ አሸናፊ፦ በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ምክንያቶች ያልተከተቡ ህጻናትን በመለየት በቂ የክትባት አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል። በዚህ ሂደት 2…
Read more

በጤናው ዘርፍ ጥራትና ደህንነት በማረጋገጥ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ

(ሆሳዕና፣ሰኔ 27/2017)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመታዊ ስራ አፈጻጸም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሔደ ነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካ አለሙ እንደገለጹት የጤና ቁጥጥር ስራ ዋነኛ አላማ ህብረተሰቡ በጤናው መስክ የሚያገኛቸው…
Read more