Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Blog

በጤና ተቋማት የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት በመዘርጋት ዘርፉን ለማዘመን መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ

(ሆሳዕና፣የካቲት 23/2017 )በጤና ሚኒስተሯ የተመራ ልዑክ በጉራጌና ሀድያ ዞኖች በጤናዉ ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ጎብኝቷል፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንዳሉት በክልሉ በጤና ተቋማት ላይ እየተካሔደ ያለው ምልከታ መልካም ልምዶችን ማስቀጠል እና በአፈጻጸም ረገድ የተስተዋሉ ውስንነቶችን ማረም የሚያስችል ነው ብለዋል። በዚህም በጉራጌና በሀድያ ዞኖች በጤናዉ ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡ በወልቂልጤ ከተማ በተለይም በመጀመሪያ…
Read more

የጤና አገልግሎት ስርዓትን ለማዘመን የበለጸጉ ሶፍትዌሮች እና በተገነቡ ጤና ተቋማት የህክምና ቁሳቁስ ለማሟላት ድጋፍ ያስፈልጋል ፦

ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው የጤና አገልግሎት ስርዓትን ለማዘመን የበለጸጉ ሶፍትዌሮች እና በተገነቡ ጤና ተቋማት የህክምና ቁሳቁስ ለማሟላት ድጋፍ ያስፈልጋል ፦ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ሆሳዕና፣የካቲት 23/2017ዓ.ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ለስራ ባልደረቦቻቸው በጽ/ቤታቸው አቀባበል አድርገዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ከልኡካን ቡድኑ ጋር…
Read more

ተላላፊ በሽታዎችን ከመከላከል አኳያ ክትባት ትልቁን ድርሻ የሚወስድ በመሆኑ በዘመቻ መልክ በሚሰጡ ተግባሮች ላይ ትኩረት እንደሚያስፈልግ ተመላከተ፡

በክልል ደረጃ ለመጀመሪያ ዙር የሚሰጠው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በቀቤና ልዩ ወረዳ ፍቃዶ ጤና ኬላ በይፋ ተጀምሯል፡፡ በማስጀመሪያው ፕሮግራም ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በዚህ ወቅት እንዳሉት ሀገራችን የምትከተለው መከላከል ላይ መሠረት ያደረገው የጤና ፖሊሲ የፋውስ ህክምና መጨመሩን አንስተዋል፡፡ የህፃናትን ሞት…
Read more

የፖሊዮ ክትባት በክልሉ ከፊታችን ዓርብ የካቲት 14-17/2017 ዓ.ም ይሰጣል

(ሆሳዕና:- የካቲት 12/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከየካቲት 14-17/2017 ዓ/ም የሚካሄደውን ክልል አቀፍ የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ለመገናኘት ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።መግለጫውን የክልሉ ጤና ቢሮና በቢሮው የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋራ ሰጥተዋል። የቢሮው ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በመግለጫቸው በክልሉ ከየካቲት 14-17/2017 ዓ/ም ክልል አቀፍ የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ(የልጅነት ልምሻ) ክትባት ይሰጣል ብለዋል። የፖሊዮ በሽታ…
Read more

የፖሊዮ በሽታን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት አመራሩ እና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

የካቲት 11/2017 የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻን አስመልክቶ ለከፍተኛ አመራሩ እና ለባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደዋል። የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ምክትል ተጠሪ አቶ ረመቶ መሀመድ እንደገለጹት የፖሊዮ በሽታን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት አመራሩ እና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ገልጸዋል። የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በአለም እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ እና በዞኑ ደረጃ…
Read more

በስልጤ ዞን ከየካቲት 14-17 ዓም ድረስ የሚካሄደውን የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ቅድመዝግጅት እና የማዕጤመ ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ

11/2017 ዓ/ም ወራቤ በማዕከላዊ ጤና ቢሮ ም/ቢሮ ሃላፊ እና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር በአቶ ማሙሽ ሁሴን አማካኝነት የተመራ የድጋፍ ቡድን ከየካቲት 14-17 ዓም እድሜአቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የሚሰጠውን የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ቅድመዝግጅት እና የማዕጤመ ተግባራት አፈፃፀም የዞኑ መንግስት ዋና ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ሃላፊ ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር እና የመምሪያው ማኔጅመነት በተገኙበት…
Read more

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ከየካቲት 14 እስከ 17/2017/ዓ.ም የሚካሄደው የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ለባለድርሻ አካላት የኦረንቴሽንና ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በመድረጉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መሰለ ጫካ የፖለቲካና ሪዮት አለም ዘርፍ ሀላፊ አቶ መሠረት ሽፋ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አህመድ ኑሪ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታሪኩ ደምሴ እንዲሁም የዞን አመራሮች የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች የጤና ፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን እና የፀጥታ…
Read more

በክልል አቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ዙሪያ ለክልሉ ጤና ቢሮ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ገለፃ ተሰጠ፡፡

ከየካቲት 14-17/2017 ዓ/ም ለ4 ተከታታይ ቀናት ዘመቻው ይካሄዳል፡፡ በዘመቻውም ከ1 ሚሊየን በላይ አድሜያቸው 5 ዓመትና ከ5 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት በጤና ባለሙያዎች አማካይነት ክትባቱን እንደሚያገኙ ተመላክቷል፡፡ ቤት ለቤት በሚሰጠው የመጀመሪያ ዙር ክልል አቀፍ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ላይ የግብአት አቅርቦት ችግር እንዳይኖር ቅድመ ዝግጅት መደረጉ በገለጻው ወቅት ተበራርቷል፡፡ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ…
Read more

በስልጤ ዞን የሚቶ ወረዳ የማህበረሰብ መድሀኒት ቤት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ::

በሚቶ ወረዳ በመንግስትና ማህበረሰብ ትብብር የተገነባውና ለማህበረሰቡ መድሃኒት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የሚጠበቀው የማህበረሰብ መድሀኒት ቤት ተመርቋል የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ ወ/ሮ ነዒማ ሙኒር፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ሀላፊና የገጠር ክላስተር አስተባባሪ በሆኑት በአቶ ኡስማን ሱሩር እና በሚቶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ…
Read more

የካቲት 9/2017 ዓ/ም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከየካቲት 14-17/2.017 ዓ/ም ድረስ ቤት ለቤት እንደሚሰጥ ተገለፀ

በክልል አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የመጀመሪያ ዙር ፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡ በክልል ደረጃ ለሚገኙ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ቡታጅራ ከተማ የአድቮኬሲ መድረክ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያ የክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደተናገሩት በክልል አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው የመጀመሪያ ዙር ፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡…
Read more