Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Author: admin

CERPHI

የአፍሪካ በሽታ መከላከያ እና መቆጣጠርያ ማዕከል የመድሃኒት እና የህክምና መሣሪያዎች አቅርቦት ለአፍሪካ ሃገራት ለመጀመር የሚረዳ አህጉራዊ የውይይት መድረክ ተካሄደ::

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ከአፍሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ጋር በመተባበር በአፍሪካ የተቀናጀ የመድሃኒት እና የህክምና መሣሪያዎች ግዢ እና አቅርቦት ሜካኒዝም ጅምር ላይ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ውይይት አካሂደዋል፡፡ ሜካኒዝሙ አፍሪካ ሲዲሲ በጋራ በሚሰበሰብ ፈንድ የመድኃኒት ምርቶችን እና ክትባቶችን በመግዛት ለአባል ሀገራት ማሰራጨት እና የሃገር ውስጥ ምርትን ለማበረታታት የሚያስችለው ነው። በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር…
Read more

ማህበረሰቡ ፣ባለሀብትና መንግስት በማስተባበር ከ190 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለጤና ተቋማት ግብዐት ማሟላት እንደተቻለም ተገለጸ።

“በባለቤትነት ላይ የተመሰረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ ” በሚል መሪ ቃል የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 ማጠቃለያ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የማህበረሰቡ ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዋነኛው አማራጭ የጤና መድህን አጋግሎት መሆኑ ተገልጿል!! በመድረኩ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣የጉራጌ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ…
Read more

ሳምንታዊ የህረተሰብ ጤና አደጋዎች ውይይት ተካሄደ ፡፡

ሳምንታዊ የህረተሰብ ጤና አደጋዎች ውይይት ተካሄደ ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና ማስተባበሪያ ማዕከል በወባ በሽታና በሌሎች የጤና ጉዳዮች ሳምንታዊ ውይይት አድርጓል። የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን በመድረኩ እንደገለጹት የወባ በሽታ ከባለፈው ሳምንት ጋር ሲነጻጸር በ32% ጭማሪ ማሳየቱን በመጠቆም በቀጣይ ጊዜያት ወቅቱን ታሳቢ…
Read more

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ የ”40″ኛ ሣምንት “EOC” በመምሪያ ደረጃ ተገመገመ።

ሪፖርቱ በአቶ እንዳለ በኩል ሰፋ ባለ መልኩ የቀረበ ሆኖ ከወባ አንፃር የ40ኛ ሣምንት 1591 case ሆኖ ከአምናው ተመሳሳይ ሣምንት ከነበረው 1955 ቁጥር አንፃር የመቀነስ አዝማምያ ያለ ቢመስልም እንኳ ከባለፈው ሣምንት (39ኛ) አንፃር 1121 የነበረ ስለነበር 466 የጨመረበት ሁኔታ እንዳለ ተብራሮቷል። ‎ ‎ከፍተኛ የወባ ቁጥር የታየባቸው ሶሮ 169(10.6%), ጎምቦራ 150(9.4%), ሾኔ 144 ሆኖ ከወባ አይነት (species)…
Read more

በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጤና ጽህፈት ቤት የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

“በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጤና ጽህፈት ቤት የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በሙዱላ ከተማ እየተካሄደ ነው። የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ “በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ እውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ስርዓት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት በ2017 ዓ.ም ዓመታዊ በሙዱላ…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከል መርቆ ከፈተ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከል መርቆ ከፈተ። የቢሮው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በሆስፒታሉ ተገኝተው የማዕከሉን ሥራ በይፋ አስጀምረዋል። ማኔጅመንቱ በሆስፒታሉ እየተሰጡ የሚገኙ የህክምና አገልግሎቶችን ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ የህብረተሰቡን ጤና ለማሻሻል በተቋሙ የተጀመሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተመልክቷል። የሆስፒታሉ ስራ-አስኪያጅ ዶ/ር ፍቅረ-ጽዮን በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት፦ ሆስፒታሉ ወደ ሥራ ከገባ…
Read more

በጤናው ዘርፍ መሻሻል እንዲመጣ የጥናትና ምርም ስራዎች ሚናቸው ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ እና የ2018 ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ በወራቤ ከተማ ተካሂዷል። ሐምሌ 8/2017 ሀላባ ቲቪ —————————- በመድረኩ ላይ ለዕለቱ የተዘጋጀ ሰነድና የአፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ምላሽና ማብራሪያውን የሰጡት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙዔል ዳርጌ በክልሉ የወባና ኮሌራ ወረርሽኝን የመቆጣጠር ልምድ እየዳበረ መምጣቱን አስታውሰው…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አመታዊ ጉባኤውን በወራቤ ከተማ እያካሄደ ነው።

(ሆሳዕና፣ ሀምሌ 8/2017)፤ ኢንስቲትዩቱ በመድረኩ የ2017 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም እና የበጀት አመቱ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተወያየ ይገኛል። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት አመት አምስት የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት በትኩረት መሠራቱን አንስተዋል። ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋንን ማፍጠን፣ የህብረተሰቡን የጤና ሁኔታን ማሻሻል፣ ህብረተሰቡን ከድንገተኛ አደጋ መጠበቅ፣ የጤና…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎ ግንባታው የተጠናቀቀውን ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ መርቆ ስራ አስጀመረ::

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በህብረተሰብ ተሳትፎና በክልሉ መንግስት ገንዘብ ወጪ የተገነባውን የንቡር ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ስራ አስጀመረ። ለሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ግንባታው የአካባቢው ህዝብና የክልሉ መንግስት ከ13ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጋቸው ተገልጿል። የጤና ተቋሙን መርቀው ስራ ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የብልጽግና መንግስት…
Read more

የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሁሉም አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ በEOC ግምገማ ላይ ተገለፀ::

በ27ተኛ ሳምንት 7ሺህ 77ሰዎች የወባ ምርመራ ከተደረገላቸዉ መካከል 1 ሺህ 6መቶ 58 ሰዎች በወባ ሲያዙ የ10 ሰዎች ተኝተው ታክመዋል፡፡ በዞኑ ያለው የወባ መገኘት ምጣኔ 23 በመቶሲሆን ፕላዝሞዲየም ፋልሲፈረም 754(46%)፣ፕላዝሞዲየም ቫይቫክስ 885(54%) መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ። በሳምንቱ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረባቸው መዋቅሮችአለም ገቢያ 269፣ ዳሎቻ ከተማ 206 ፣ ሳንኩራ ወረዳ 189 ፣ ምስራቅስልጢ ወረዳ 171 ፣ሁልባራግ ወረዳ 161…
Read more