Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Author: admin

CERPHI

የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ

ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሚገኘዉ በሺንሽቾ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩም የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወባ በሽታ ምልክቶችና መተላለፊያ መንገዶች እንዲሁም የበሽታዉ መከላከያ መንገዶች ዙርያ ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ የተሰጠ መሆኑን ተገልጿል።

የወባ በሽታ ወረርሽኝ አሁን ካለበት ስርጭት ደረጃ ከፍ እንዳይል የሁሉም አመራር እና የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።

ጥቅምት 5/2017 የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ሳምንታዊ የ (EOC)የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምለሽ አሰጣጥ ሳምንታዊ አፈፃፀምና ወቅታዊ የወባ በሽታ ስርጭትን አስመልክቶ ውይይት በዛሬው እለት ተካሂዷል። የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምለሽ አሰጣጥ እና የማህበረሰብ ጤና አደጋዎችና የወባ ወረርሽኝ ምላሽ መስጠት ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ተደርጓል። በመድረኩም በዞናችን ስር በሚገኙ በሁሉም መዋቅሮች የወባ ወረርሽኝ በተከሰተባቸዉ ቀበሌያት የበሽታውን ሥርጭት…
Read more

የወባ በሽታ የሚያሳድረውን ሁለንተናዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥተው ርብርብ ሊያደርጉ እንደሚገባ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ገለፁ!

ዋና አስተዳዳሪው ይህን ያሉት የዞኑ ጤና መምሪያ የወባ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው ሲል ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቦታል።

ከደቡብ እና ማዕከላዊ ኢትዮዽያ መሠረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና ያጠናቀቁ ባለሙያዎች ሰርተፍኬት ተቀበሉ

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል የዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ከኢንስቲትዩቱ ብሔራዊ የስልጠና ማዕከል ጋር በመተባበር ከደቡብ እና ማዕከላዊ ኢትዮዽያ ተውጣጥተው በሶስት ዙር የተሰጠውን መሰረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና (Frontline-FETP) ያጠናቀቁ 27 የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች ዛሬ ጥቅምት 3/2017 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ አስመረቀ፡፡ አቶ አወል ዳውድ የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ባለሙያ እና…
Read more

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ሣምንታዊ የEOC ግምገማ አካሂዷል

የወባ በሽታ ስርጭትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር እንዲቻል ለማድረግ ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ ማህበረሰቡ ድረስ የመከላከልና የቁጥጥር ሥራ ላይ በንቃት ማሳተፍ እንደሚገባ ተገልጿል። የወባ በሽታ በህብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖና ጫና ለመከላከልና ለመቆጣጠር በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት የሚያደርጉት ርብርብ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላክቷል ። የወባ መከላከል ተግባራትን ለማጠናከር በወረዳዎች የተሰራ በድጋፍና ክትትል የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ…
Read more

ጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጥናት ለሚያደርግ የጥናት ቡድን ስምሪት መሰጠቱ ተገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ለጥናታዊ ቡድኑ የስራ ስምሪት በሰጡበት ወቅት ጥናቱ በክልሉ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች በ39 ጤና ጣቢያዎች በ10 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች እና በ3 አጠቃላይ ሆስፒታሎች በጥናት የተደገፈ ተግባር የሚፈጽም መሆኑን አስረድተዋል። የሰው ሀይል ውጤታማነት፣ የግብአት እና የመድሀኒት አቅርቦት እንዲሁም አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ስርአት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እንዲሁም በጤና ተቋማት የሚታዪ…
Read more

በስልጢ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት የወባ በሽታ ስርጭት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ህብረተሰቡን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

በስልጢ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት የወባ በሽታ ስርጭት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ህብረተሰቡን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በአገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ቁጥር አንድ የሰው ልጆችን ገዳይ በሽታ እንደሆነ የሚታወቀው የወባ በሽታ በወረርሽኝ መልክ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ለብዙሃን ሞት ምክንያትም ሆኗል፡፡ በሽታው በአገር ኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ኑሮና በፖለቲካው ላይ የሚያስከትለው ቀውስ በቀላሉ የሚገመት አይደለም ስለሆነም በሽታው በአብዛኛው በህፃናት፣…
Read more

የተደራጀ የጤና ልማት ሰራዊት በመጠቀም የወባ በሽታን መከላከል እንደሚገባ የስልጢ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ!

የተደራጀ የጤና ልማት ሰራዊት በመጠቀም የወባ በሽታን መከላከል እንደሚገባ የስልጢ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ! ሐምሌ 21/2016 የስልጢ ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን የስልጢ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የተደራጀ የጤና ልማት ሰራዊትን በመጠቀም የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎች በማፋሰስና በማዳፈን ትንኝ እንዳይራባ ማድረግ በሚሉ መሪ ሀሳቦች ከዘርፉ ባለሙያዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ወቅቱን ተከትሎ ሊከሰት የሚችል የወባ…
Read more

መገናኛ ብዙሀን ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ

መገናኛ ብዙሀን ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ጤና ቢሮ ወቅታዊ የወባ በሽታን አስመልክቶ ከሚዲያ አካላት ጋር በወራቤ ከተማ ውይይት አካሄደ። የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አማካሪ አቶ ሀብቴ ገብረሚካኤል እንደሀገር እና ክልል የተከሰተው የወባ ወረርሽኝ የህብረተሰቡ ጤና ስጋት እንዳይሆን ማህበረሰቡን የማንቃት ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ክልሉን እንደ…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት መረጃዎችንና ምላሽ ስራን የሚያስተባብሩ ማዕከላትን በማቋቋም የወባ ስርጭትን ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት መረጃዎችንና ምላሽ ስራን የሚያስተባብሩ ማዕከላትን በማቋቋም የወባ ስርጭትን ለመቀነስ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን ከሚዲያዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ መረጃዎችንና ምላሽ ስራን የሚያስተባብር ማዕከላትን በማቋቋም የወባ ስርጭትን ለመቀነስ እየሰራ ነው። ማዕከላት በክልሉ ሰባቱም ክላስተሮች መቋቋማቸውን በመግለጽ ወባን ጨምሮ ሌሎችም ወረርሽኞችን ጭምር መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ሀሳብ…
Read more