
የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች የጤና ስርዓታችን የጀርባ አጥንት እና በጤና ተቋማት እና በማህበረሰቦች መካከል ያሉ ድልድይ ናቸው” ያሉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፤ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች ለተሻሻለ የጤና ውጤት ብቻ ሳይሆን ለስራ ዕድል፤ ለማብቃት እና ለዕድገት አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል።
የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ ስርዓቶችን በማጠናከር እና ለህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ በመስጠት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናግረዋል።
የማስተርካርድ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት ሰዊት አህደሮም የፋውንዴሽኑን የያንግ አፍሪካ ስራዎች ስትራቴጂ እና በተለይም በአፍሪካ በሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ላይ በማተኮር ለጤና የሰው ኃይል ልማት ያለውን ቁርጠኝነት አጉልተው አሳይተዋል።
በዝቅተኛ ደረጃዎች ያሉ የጋራ የትግበራ ማዕቀፎችን መደገፍ፣ በዘላቂ ፋይናንስ ላይ ስምምነት ማድረግ እና ግልጽ የሆኑ ደረጃዎች እና የአስተዳደር ዝግጅቶች ያሉት የ90 ቀናት የድርጊት መርሃ ግብር ማዘጋጀት ከመድረኩ እንደሚጠበቅ የማስተርካርድ ፋውንዴሽን የኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር መፍትሄ ታደሰ ገልጸዋል።
ጤና ሚኒስቴር እና ማስተርካርድ ፋውንዴሽን የአፍሪካን የጤና ኤክስቴንሽን የሰው ኃይል ማጠናከር፡ አሰላለፍ፣ አተገባበር እና ዘላቂነት” በሚል መሪ ቃል ከ20 በላይ የአፍረካ ሃገራት የተውጣጡ የጤና ዘርፍ መሪዎችን፣ አጋሮችን፣ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን እና የፋይናንስ ድርጅቶችን አሰባስቧል።
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia
Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB



