Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

ኢትዮጵያ ሦስተኛውን የአፍሪካ የህክምና ግብዓት ምርት ኮንፍረንስ እና ኤግዚቢሽን (AHMTEC-2026) ታዘጋጃለች

ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያደረገች ባለችው ለውጥ በተለይም በመሰረተ-ልማት አቅርቦት፣ለቱሪዝም ምቹ በመሆን፣ለስብሰባ ምቹ የሆኑ አዳራሾችን እየገነባን እንዲሁም ለኢንቨስትመንት አመቺ የሆኑ ፖሊሲዎች እየተፈጠሩ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመጣ እድል መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ናቸው።

ሁለተኛው ኤግዚቢሽን በባለፈው ዓመት በጋና በተካሄደ ወቅት ሦስተኛውን የአፍሪካ የህክምና ግብዓት ምርት ኮንፍረንስ እና ኤግዚቢሽን ከብዙ ሃገሮች ጋር ተወዳድራ ኢትዮጵያ ካሏት ምቹ ሁኔታዎች አንፃር የተመረጠች መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ ፍሬህይወት በኤግዚቢሽኑ ከስድስት መቶ በላይ ኢንቬስተሮች፣የፋይናንስ ተቋማት፣ተቆርቋሪዎች፣የፈጠራ እና የምርምር ባለሙያዎች እንዲሁም አምራቾች የሚሳተፉበት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ወ/ሮ ፍሬህይወት አክለውም አፍሪካ እንደ አህጉር ሰባ በመቶ (70%) የሚሆነውን መድሀኒትና የህክምና ግብዓት ከተለያዩ አለም ሃገራት እንደምታስገባ ገልጸው በክትባት ረገድም አንድ በመቶውን (1%) ብቻ ነው በማምረት እየሸፈነች ያለው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ይህንን ኤግዚቢሽን በማዘጋጀቷ የአፍሪካን የገበያ ድርሻ በተሻለ መልኩ ማግኘት ያስችላታል፣ ኢንቨስተሮችን ለመሳብ እንዲሁም በስፋት እየተሰራበት ያለውን ኢትዮጵያን የፋርመሲቱካል ሀብ የማድረግ ጥረት በብዙ መንገድ ያግዛል ብለዋል ወ/ሮ ፍሬህይወት።

በመጨረሻም ወ/ሮ ፍሬህይወት መገናኛ ብዙሃን ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ኢትዮጵያ ያላትን ዘርፈ ብዙ መልካም አጋጣሚዎችን በስፋት ለዓለም የማሳወቅ ስራ እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Website: moh.gov.et

Facebook: Ministry of Health,Ethiopia

Twitter: x.com/fmohealth

YouTube: youtube.com/@FMoHealthEthiopia

Tiktok: tiktok.com/@mohethiopia

Telegram: t.me/M0H_EThiopia

Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *