Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Blog

ወቅታዊ ጉንፋን እና ጉንፋን መሰል የመተፈንሻ አካላት ህመም በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ

የጉንፋን ሕመም በተፈጥሮ የላይኛውን የመተንፈሻ የሰውነት ክፍሎች ማለትም አፍንጫን፣ ጎሮሮን እና የአየር መተላለፊያ ባንቧን የሚያጠቃ ተላላፊ ሕመም ነዉ። ሪኖ ቫይረስ ለጉንፉን መከሰት ዋና ምክንያት ሲሆን፣ ኮሮና፣ ኢንፍሉዌንዛ፣ ፓራ ኢንፍሉዌንዛ፣ አር ኤስ ቪ(RSV) ቫይረሶች ደግሞ ለጉንፉን መሰል ህመሞች መከሰት ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸዉ። ከተጠቀሱት ቫይረሶችም ለጉንፋን ሕመም መከሰት 50 በመቶ ድርሻውን የሚይዘው ሪኖ ቫይረስ ነው፡፡ በደረቅ…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ኤች እይቪ ቫይረስን ጨምሮ ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ላይ የሚፈጠረውን የቫይረስ ጉዳት ለመቀነስ የላብራቶሪ የአሰራር ሂደቶችን ጥራት ማሻሻል እንደሚገባ ተጠቆመ።

ኢንስቲትዩቱ ከህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ እና ከዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ጋር በጋራ ለኤች አይቪ ቫይረስ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የቫይራል ሎድ መጠንን ለመቀነስ በሚያስችሉ ሁኔታዎች እና የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ዜዴዎች ዙሪያ ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር መክሯል ። አቶ አለማየሁ ጌታቸው የቢሮው ዘርፈ ብዙ የኤች አይቪ ኤድስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኤች አይቪ ኤድስ…
Read more

እየተባባሰ የመጣውን የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በትኩረት ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ የሚቶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር መሀመድ አሳሰቡ!

ጥቅምት 07/2017 ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን በሰልጤ ዞን የሚቶ ወረዳ የወባ በሽታ አጭር ጊዜ ውስጥ ለመግታት የሚያስችል ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሄደ። የሚቶ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ከድር መሀመድ እንደገለፁት የወባ በሽታ መከላከል ስራዎች በተገቢው እንዲከናወን ህብረተሰቡን ያሳተፈ ንቅናቄ ስራዎች እንዲከናወን አሳስበዋል። ዋና አሰተዳዳሪው በሽታው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ በሁሉም ቀበሌያት ከወትሮው…
Read more

የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ

ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሚገኘዉ በሺንሽቾ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩም የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወባ በሽታ ምልክቶችና መተላለፊያ መንገዶች እንዲሁም የበሽታዉ መከላከያ መንገዶች ዙርያ ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ የተሰጠ መሆኑን ተገልጿል።

የወባ በሽታ ወረርሽኝ አሁን ካለበት ስርጭት ደረጃ ከፍ እንዳይል የሁሉም አመራር እና የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።

ጥቅምት 5/2017 የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ሳምንታዊ የ (EOC)የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምለሽ አሰጣጥ ሳምንታዊ አፈፃፀምና ወቅታዊ የወባ በሽታ ስርጭትን አስመልክቶ ውይይት በዛሬው እለት ተካሂዷል። የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምለሽ አሰጣጥ እና የማህበረሰብ ጤና አደጋዎችና የወባ ወረርሽኝ ምላሽ መስጠት ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ተደርጓል። በመድረኩም በዞናችን ስር በሚገኙ በሁሉም መዋቅሮች የወባ ወረርሽኝ በተከሰተባቸዉ ቀበሌያት የበሽታውን ሥርጭት…
Read more

የወባ በሽታ የሚያሳድረውን ሁለንተናዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥተው ርብርብ ሊያደርጉ እንደሚገባ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ገለፁ!

ዋና አስተዳዳሪው ይህን ያሉት የዞኑ ጤና መምሪያ የወባ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው ሲል ስልጤ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቦታል።

ከደቡብ እና ማዕከላዊ ኢትዮዽያ መሠረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና ያጠናቀቁ ባለሙያዎች ሰርተፍኬት ተቀበሉ

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል የዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ከኢንስቲትዩቱ ብሔራዊ የስልጠና ማዕከል ጋር በመተባበር ከደቡብ እና ማዕከላዊ ኢትዮዽያ ተውጣጥተው በሶስት ዙር የተሰጠውን መሰረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና (Frontline-FETP) ያጠናቀቁ 27 የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች ዛሬ ጥቅምት 3/2017 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ አስመረቀ፡፡ አቶ አወል ዳውድ የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ባለሙያ እና…
Read more

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ሣምንታዊ የEOC ግምገማ አካሂዷል

የወባ በሽታ ስርጭትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር እንዲቻል ለማድረግ ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ ማህበረሰቡ ድረስ የመከላከልና የቁጥጥር ሥራ ላይ በንቃት ማሳተፍ እንደሚገባ ተገልጿል። የወባ በሽታ በህብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖና ጫና ለመከላከልና ለመቆጣጠር በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት የሚያደርጉት ርብርብ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላክቷል ። የወባ መከላከል ተግባራትን ለማጠናከር በወረዳዎች የተሰራ በድጋፍና ክትትል የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ…
Read more

ጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጥናት ለሚያደርግ የጥናት ቡድን ስምሪት መሰጠቱ ተገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ ለጥናታዊ ቡድኑ የስራ ስምሪት በሰጡበት ወቅት ጥናቱ በክልሉ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች በ39 ጤና ጣቢያዎች በ10 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች እና በ3 አጠቃላይ ሆስፒታሎች በጥናት የተደገፈ ተግባር የሚፈጽም መሆኑን አስረድተዋል። የሰው ሀይል ውጤታማነት፣ የግብአት እና የመድሀኒት አቅርቦት እንዲሁም አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ስርአት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እንዲሁም በጤና ተቋማት የሚታዪ…
Read more

በስልጢ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት የወባ በሽታ ስርጭት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ህብረተሰቡን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

በስልጢ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት የወባ በሽታ ስርጭት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ህብረተሰቡን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በአገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ቁጥር አንድ የሰው ልጆችን ገዳይ በሽታ እንደሆነ የሚታወቀው የወባ በሽታ በወረርሽኝ መልክ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ለብዙሃን ሞት ምክንያትም ሆኗል፡፡ በሽታው በአገር ኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ኑሮና በፖለቲካው ላይ የሚያስከትለው ቀውስ በቀላሉ የሚገመት አይደለም ስለሆነም በሽታው በአብዛኛው በህፃናት፣…
Read more