Central Ethiopia,Worabe
cerphi@cerphi.gov.et

Blog

CERPHI

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አሃድ የንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አሃድ የንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው የንቅናቄ መድረኩን በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ያለው። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ መድረኩን ባስጀመሩበት ጊዜ እንዳሉት ዘርፈ ብዙ ማህበራዊ ብልጽግና ሊያረጋግጡ ከሚችሉ ቁልፍ ተግባራቶች ዋናው የጤና ሥርዓት ማሻሻል ነው። በዚህም…
Read more

የእናቶችና ህጻናት ሞትና የሞት መንስኤዎችን አስመልከክቶ የናሙና ምዝገባ ሥርዓት የማስጀመሪያ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈረመ::

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል ከክልል ጤና ቢሮዎች እና ከሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ጋር የእናቶችና ህጻናት ሞት እና የሞት መንስኤዎች እንዲሁም አጠቃላይ የበሽታ ሰርጭት የመለየት እና ያሉትን የክትትል ስርዓቶችን ለማጠናከር የናሙና ምዝገባ ስርዓትን (Sample Registration System/SRS/) ለመዘርጋት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን የማስጀመሪያ የዉይይት መድረክም ሰኔ 24/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ…
Read more

የማ/ኢ/ጤና ቢሮ እና የህ/ጤ/ኢ የተቀናጀ የኩፍኝ እና ፖሊዮ ክትባት፤ ስርአተ ምግብ፤ እናቶች እና ህጻናት ጤና አገልግሎት ዘመቻ እንዲሳካ ላደረጉት ጥረት እውቅና ተሰጣቸው

የማእከላዊ ኢትዩጲያ ክልል ጤና ቢሮ እና የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የተቀናጀ የኩፍኝ እና ፖሊዮ ክትባት፤ ስርአተ ምግብ፤ እናቶች እና ህጻናት ጤና አገልግሎት ዘመቻ እንዲሳካ ላደረጉት ጥረት እውቅና ተሰጣቸው ! ___________ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የኩፍኝና የፖሊዮ ክትባት፣ሥነ-ምግብ እና የእናቶችና ሕጻናት ጤና አገልግሎት ዘመቻዎች ስኬታማ መሆናቸውን ለመገምገምና እውቅና ለመስጠት ልዩ ስብሰባ ተካሂዷል። ዝግጅቱ ያተኮረው በግንቦት ወር በሀገር አቀፍ ደረጃ…
Read more

ውል የተገባለት የመድኃኒት ፍላጎት እና አቅርቦት ሥርዓት አተገባበር ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት አለባቸው

ውል የተገባለት የመድኃኒት ፍላጎት እና አቅርቦት ሥርዓት አተገባበር ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት አለባቸው አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፦ ውል የተገባለት የመድኃኒት ፍላጎት እና አቅርቦት ሥርዓት አተገባበር ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ በባህል እና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡረቃ(ዶ/ር) አስገነዘቡ። ውል የተገባለት የመድኃኒት ፍላጎት…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ hope SBH ከተባለ አጋር ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ ፡

በክልሉ በተፈጥሮ ከመጠን በላይ የፈሳሽ ክምችት እና የነርቭ ዘንግ ክፍተት ተጠቂ የሆኑ ህጻናት ህክምና እና ድጋፍ እንዲያገኙ የሚያስችል ስምምነት መሆኑ ተገልጿል ፡፡ ስምምነቱን በማስመልከት ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በክልሉ በተፈጥሮ የጤና ችግር ያለባቸው ህጻናት ፈጣን ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል ፡፡ በተለይም በተፈጥሮ የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ…
Read more

ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ – ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ

ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ – ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ (ሆሳዕና፣ ሰኔ 20/2017)፦ በኢትዮጵያ ለሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት አዳዲስ የኢኖቬሽን ስራዎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተናገሩ። “ኢኖቬሽን ለሁለንተናዊ የጤና ሽፋን” በሚል መሪ ሃሳብ ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሔድ የነበረው አለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ ተጠናቋል። የጤና…
Read more

የምግብ ደህንነትን በማረጋገጥ በአካልና በአእምሮ ላይ የሚያጋጥመንን የጤና እክል መከላከል ይገባል – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ

(ሆሳዕና:- ሰኔ 20/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በክልሉ በሚገኙ የዱቄትና ዱቄት ውጤት አምራቾች ጋር በንጥረ ነገር የበለፀገ ምርት ማምረት የሚያስችል የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እያካሄደ ነው። የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ የምግብ ደህንነትን በማረጋገጥ በአካልና በአእምሮ ላይ የሚያጋጥመንን የጤና እክል…
Read more

ፈጠራን ባሕል በማድረግ የሕክምና ዘርፉን መደገፍ ይገባል

ፈጠራን ባሕል በማድረግ የሕክምና ዘርፉን መደገፍ ይገባል ሲሉ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ ገልጸዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽን እና ጥራት ጉባኤ ዛሬ 2ኛ ቀኑን ይዟል። በጉባኤው ላይ “ፈጠራ ሁሌም ጥራትን ለማምጣት ይረዳል” ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ፈጠራ የታከለበት ስራ የጤና ዘርፉን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል አመላክተዋል። በኢትዮጵያ የጤና ተደራሽነትና ጥራት ላይ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው፤ ጥራት…
Read more

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ የድጋፍ እና ክትትል ስምሪት ሰጠ ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የሚቆይ የድጋፍ እና ክትትል ስምሪት ሰጠ ፡፡ የ2017 የሁለተኛ ግማሽ ዓመት ማጠቃለያ ድጋፋዊ ክትትል ከ16/10/17 ዓ/ም ጀምሮ ከዞን እና ልዩ ወረዳ ጀምሮ እስከ እስከ ታች ጤና ተቋማት በመውረድ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት የድጋፍ ክትትል ስራ እንደሚሰራ በኦረንቴሽኑ ተገልጿል ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ…
Read more

በክልሉ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል ደህንነቱ የተጠበቀና አሰተማማኝ መረጃ ላይ የተመሰረተ ዉሳኔን ተጠቅሞ አዲስ ግኝት ለማዘጋጀት የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።

የማዕ/ ኢት/ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የጥናት እና ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የመረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል በክልሉ ጤና ቢሮ የህብ/ ጤና ኢን/ት እንዲሁም ከዩኒቨርስቲና ኮሌጅ ለተወጣጡ ባሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው ። በጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጥናት እና ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ስናፍቅሽ አየለ እንደተናገሩት የጤና መረጃ አስተዳደር…
Read more